የትከሻ መድረቅ (Frozen Shoulder)
ፍሮዝን ሾልደር (የትከሻ መድረቅ ) በትከሻ አካባቢ ከሚታዩ ችግሮች አንዱ ሲሆን በትከሻ ላይ ህመም እና መድረቅን ያስከትላል፡፡
ፍሮዝን ሾልደር በማን ላይ ይታያል?
- እድሜያቸው ከ40 አመት በላይ የሆኑ ሰዎች
- በሴቶች በተለይ ይታያል
- በተለያዩ ምክንያቶች ትከሻ ረዘም ላለ ጊዜ ሳይንቀሳቀስ ሲቀር (ለምሳሌ በትከሻ ጉዳት/ ቀዶ ህክምና)
- ተጓዳኝ በሽታ ያላቸው (ለምሳሌ ስኳር ፣ ታይሮይድ)
ምልክቱ
ሶስት ደረጃዎች ሲኖሩት የመጀመሪያው ትከሻ ሲንቀሳቀስ ህመም መሰማት ሲሆን ሁለተኛው ትከሻ መድረቅ ወይም ማንቀሳቀስ መቸገር ነው፡፡ በሶስተኛው ደረጃ ላይ በህመም እና ትከሻ ድርቀት ላይ ማገገም ይታያል፡፡
ህክምናው
- ፊዚዮቴራፒ
- በትከሻ የሚሰጥ መርፌ
ተመሳሳይ ችግር ካለዎት በአጥንት ስፔሻሊስት ሀኪማችን ጋር ቀርበው ይታዩ።
